| 1 |
ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087001.mp3
|
سَبِّحِ اسْمَ رَبِّكَ الْأَعْلَى |
| 2 |
የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087002.mp3
|
الَّذِي خَلَقَ فَسَوَّى |
| 3 |
የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087003.mp3
|
وَالَّذِي قَدَّرَ فَهَدَى |
| 4 |
የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087004.mp3
|
وَالَّذِي أَخْرَجَ الْمَرْعَى |
| 5 |
(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087005.mp3
|
فَجَعَلَهُ غُثَاء أَحْوَى |
| 6 |
(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087006.mp3
|
سَنُقْرِؤُكَ فَلَا تَنسَى |
| 7 |
አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087007.mp3
|
إِلَّا مَا شَاء اللَّهُ إِنَّهُ يَعْلَمُ الْجَهْرَ وَمَا يَخْفَى |
| 8 |
ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087008.mp3
|
وَنُيَسِّرُكَ لِلْيُسْرَى |
| 9 |
ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087009.mp3
|
فَذَكِّرْ إِن نَّفَعَتِ الذِّكْرَى |
| 10 |
(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087010.mp3
|
سَيَذَّكَّرُ مَن يَخْشَى |
| 11 |
መናጢውም ይርቃታል፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087011.mp3
|
وَيَتَجَنَّبُهَا الْأَشْقَى |
| 12 |
ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087012.mp3
|
الَّذِي يَصْلَى النَّارَ الْكُبْرَى |
| 13 |
ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087013.mp3
|
ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحْيَى |
| 14 |
የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087014.mp3
|
قَدْ أَفْلَحَ مَن تَزَكَّى |
| 15 |
የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087015.mp3
|
وَذَكَرَ اسْمَ رَبِّهِ فَصَلَّى |
| 16 |
ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087016.mp3
|
بَلْ تُؤْثِرُونَ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا |
| 17 |
መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087017.mp3
|
وَالْآخِرَةُ خَيْرٌ وَأَبْقَى |
| 18 |
ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087018.mp3
|
إِنَّ هَذَا لَفِي الصُّحُفِ الْأُولَى |
| 19 |
በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/087019.mp3
|
صُحُفِ إِبْرَاهِيمَ وَمُوسَى |