Al-Inshiqaq

Change Language
Change Surah
Change Recitation

Amharic: Muhammed Sadiq and Muhammed Sani Habib

Play All
# Translation Ayah
1 ሰማይ በተቀደደች ጊዜ፤ إِذَا السَّمَاء انشَقَّتْ
2 ለጌታዋም (ትዕዛዝ) በሰማች ጊዜ፤ (ልትሰማ) ተገባትም፤ وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ
3 ምድርም በተለጠጠች ጊዜ፤ وَإِذَا الْأَرْضُ مُدَّتْ
4 በውስጧ ያለውንም ሁሉ በጣለችና ባዶ በኾነች ጊዜ፤ وَأَلْقَتْ مَا فِيهَا وَتَخَلَّتْ
5 ለጌታዋም በሰማች ጊዜ፤ (መስማት) ተገባትም፤ (ሰው ሁሉ ሥራውን ይገናኛል)፡፡ وَأَذِنَتْ لِرَبِّهَا وَحُقَّتْ
6 አንተ ሰው ሆይ! አንተ ጌታህን (በሞት) እስከምትገናኝ ድረስ ልፋትን ለፊ ነህ፤ ተገናኚውም ነህ፡፡ يَا أَيُّهَا الْإِنسَانُ إِنَّكَ كَادِحٌ إِلَى رَبِّكَ كَدْحًا فَمُلَاقِيهِ
7 መጽሐፉን በቀኙ የተሰጠ ሰውማ፤ فَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ بِيَمِينِهِ
8 በእርግጥ ቀላልን ምርመራ ይመረመራል፡፡ فَسَوْفَ يُحَاسَبُ حِسَابًا يَسِيرًا
9 ወደ ቤተሰቦቹም ተደሳች ኾኖ ይመለሳል፡፡ وَيَنقَلِبُ إِلَى أَهْلِهِ مَسْرُورًا
10 መጽሐፉን በጀርባው ኋላ የተሰጠ ሰውማ፤ وَأَمَّا مَنْ أُوتِيَ كِتَابَهُ وَرَاء ظَهْرِهِ
11 (ዋ! ጥፋቴ በማለት) ጥፋትን በእርግጥ ይጠራል፡፡ فَسَوْفَ يَدْعُو ثُبُورًا
12 የተጋጋመች እሳትንም ይገባል፡፡ وَيَصْلَى سَعِيرًا
13 እርሱ በቤተሰቡ ውስጥ ተደሳች ነበርና፡፡ إِنَّهُ كَانَ فِي أَهْلِهِ مَسْرُورًا
14 እርሱ (ወደ አላህ) የማይመለስ መኾኑን አስቧልና፡፡ إِنَّهُ ظَنَّ أَن لَّن يَحُورَ
15 አይደለም (ይመለሳል)፡፡ ጌታው በእርሱ (መመለስ) ዐዋቂ ነበር፤ (ነውም)፡፡ بَلَى إِنَّ رَبَّهُ كَانَ بِهِ بَصِيرًا
16 አትካዱ፤ በወጋገኑ እምላለሁ፡፡ فَلَا أُقْسِمُ بِالشَّفَقِ
17 በሌሊቱም በሰበሰውም ሁሉ፤ وَاللَّيْلِ وَمَا وَسَقَ
18 በጨረቃውም በሞላ ጊዜ (እምላለሁ)፡፡ وَالْقَمَرِ إِذَا اتَّسَقَ
19 ከኹነታ በኋላ ወደ ሌላ ኹነታ ትለዋወጣላችሁ፡፡ لَتَرْكَبُنَّ طَبَقًا عَن طَبَقٍ
20 የማያምኑት ለእነርሱ ምን አላቸው? فَمَا لَهُمْ لَا يُؤْمِنُونَ
21 በእነርሱም ላይ ቁርኣን በተነበበ ጊዜ የማይሰግዱት፤ (ምንአላቸው?) وَإِذَا قُرِئَ عَلَيْهِمُ الْقُرْآنُ لَا يَسْجُدُونَ
22 በእርግጡ እነዚያ የካዱት (በትንሣኤ) ያስተባብላሉ፡፡ بَلِ الَّذِينَ كَفَرُواْ يُكَذِّبُونَ
23 አላህም (በልቦቻቸው) የሚቆጥሩትን ዐዋቂ ነው፡፡ وَاللَّهُ أَعْلَمُ بِمَا يُوعُونَ
24 በአሳማሚ ቅጣትም አብስራቸው፡፡ فَبَشِّرْهُم بِعَذَابٍ أَلِيمٍ
25 ግን እነዚያ ያመኑና መልካሞችን የሠሩ ለእነርሱ የማይቆረጥ ምንዳ አልላቸው፡፡ إِلَّا الَّذِينَ آمَنُواْ وَعَمِلُواْ الصَّالِحَاتِ لَهُمْ أَجْرٌ غَيْرُ مَمْنُونٍ
;