Al-Mutaffife

Change Language
Change Surah
Change Recitation

Amharic: Muhammed Sadiq and Muhammed Sani Habib

Play All
# Translation Ayah
1 ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡ وَيْلٌ لِّلْمُطَفِّفِينَ
2 ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡ الَّذِينَ إِذَا اكْتَالُواْ عَلَى النَّاسِ يَسْتَوْفُونَ
3 ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡ وَإِذَا كَالُوهُمْ أَو وَّزَنُوهُمْ يُخْسِرُونَ
4 እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን? أَلَا يَظُنُّ أُولَئِكَ أَنَّهُم مَّبْعُوثُونَ
5 በታላቁ ቀን፡፡ لِيَوْمٍ عَظِيمٍ
6 ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡ يَوْمَ يَقُومُ النَّاسُ لِرَبِّ الْعَالَمِينَ
7 በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡ كَلَّا إِنَّ كِتَابَ الفُجَّارِ لَفِي سِجِّينٍ
8 ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ? وَمَا أَدْرَاكَ مَا سِجِّينٌ
9 የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡ كِتَابٌ مَّرْقُومٌ
10 ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡ وَيْلٌ يَوْمَئِذٍ لِّلْمُكَذِّبِينَ
11 ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡ الَّذِينَ يُكَذِّبُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ
12 በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡ وَمَا يُكَذِّبُ بِهِ إِلَّا كُلُّ مُعْتَدٍ أَثِيمٍ
13 አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡ إِذَا تُتْلَى عَلَيْهِ آيَاتُنَا قَالَ أَسَاطِيرُ الْأَوَّلِينَ
14 ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡ كَلَّا بَلْ رَانَ عَلَى قُلُوبِهِم مَّا كَانُوا يَكْسِبُونَ
15 ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡ كَلَّا إِنَّهُمْ عَن رَّبِّهِمْ يَوْمَئِذٍ لَّمَحْجُوبُونَ
16 ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡ ثُمَّ إِنَّهُمْ لَصَالُوا الْجَحِيمِ
17 ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡ ثُمَّ يُقَالُ هَذَا الَّذِي كُنتُم بِهِ تُكَذِّبُونَ
18 በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡ كَلَّا إِنَّ كِتَابَ الْأَبْرَارِ لَفِي عِلِّيِّينَ
19 ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ? وَمَا أَدْرَاكَ مَا عِلِّيُّونَ
20 የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡ كِتَابٌ مَّرْقُومٌ
21 ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡ يَشْهَدُهُ الْمُقَرَّبُونَ
22 እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡ إِنَّ الْأَبْرَارَ لَفِي نَعِيمٍ
23 በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡ عَلَى الْأَرَائِكِ يَنظُرُونَ
24 በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡ تَعْرِفُ فِي وُجُوهِهِمْ نَضْرَةَ النَّعِيمِ
25 ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡ يُسْقَوْنَ مِن رَّحِيقٍ مَّخْتُومٍ
26 ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡ خِتَامُهُ مِسْكٌ وَفِي ذَلِكَ فَلْيَتَنَافَسِ الْمُتَنَافِسُونَ
27 መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡ وَمِزَاجُهُ مِن تَسْنِيمٍ
28 ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡ عَيْنًا يَشْرَبُ بِهَا الْمُقَرَّبُونَ
29 እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ أَجْرَمُوا كَانُواْ مِنَ الَّذِينَ آمَنُوا يَضْحَكُونَ
30 በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡ وَإِذَا مَرُّواْ بِهِمْ يَتَغَامَزُونَ
31 ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡ وَإِذَا انقَلَبُواْ إِلَى أَهْلِهِمُ انقَلَبُواْ فَكِهِينَ
32 ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡ وَإِذَا رَأَوْهُمْ قَالُوا إِنَّ هَؤُلَاء لَضَالُّونَ
33 በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡ وَمَا أُرْسِلُوا عَلَيْهِمْ حَافِظِينَ
34 ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡ فَالْيَوْمَ الَّذِينَ آمَنُواْ مِنَ الْكُفَّارِ يَضْحَكُونَ
35 በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡ عَلَى الْأَرَائِكِ يَنظُرُونَ
36 ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡ هَلْ ثُوِّبَ الْكُفَّارُ مَا كَانُوا يَفْعَلُونَ
;