| 1 |
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079001.mp3
|
وَالنَّازِعَاتِ غَرْقًا |
| 2 |
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079002.mp3
|
وَالنَّاشِطَاتِ نَشْطًا |
| 3 |
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079003.mp3
|
وَالسَّابِحَاتِ سَبْحًا |
| 4 |
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079004.mp3
|
فَالسَّابِقَاتِ سَبْقًا |
| 5 |
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079005.mp3
|
فَالْمُدَبِّرَاتِ أَمْرًا |
| 6 |
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079006.mp3
|
يَوْمَ تَرْجُفُ الرَّاجِفَةُ |
| 7 |
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079007.mp3
|
تَتْبَعُهَا الرَّادِفَةُ |
| 8 |
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079008.mp3
|
قُلُوبٌ يَوْمَئِذٍ وَاجِفَةٌ |
| 9 |
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079009.mp3
|
أَبْصَارُهَا خَاشِعَةٌ |
| 10 |
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079010.mp3
|
يَقُولُونَ أَئِنَّا لَمَرْدُودُونَ فِي الْحَافِرَةِ |
| 11 |
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)» |
/content/ayah/audio/hudhaify/079011.mp3
|
أَئِذَا كُنَّا عِظَامًا نَّخِرَةً |
| 12 |
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079012.mp3
|
قَالُوا تِلْكَ إِذًا كَرَّةٌ خَاسِرَةٌ |
| 13 |
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079013.mp3
|
فَإِنَّمَا هِيَ زَجْرَةٌ وَاحِدَةٌ |
| 14 |
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079014.mp3
|
فَإِذَا هُم بِالسَّاهِرَةِ |
| 15 |
የሙሳ ወሬ መጣልህን? |
/content/ayah/audio/hudhaify/079015.mp3
|
هَلْ أتَاكَ حَدِيثُ مُوسَى |
| 16 |
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079016.mp3
|
إِذْ نَادَاهُ رَبُّهُ بِالْوَادِ الْمُقَدَّسِ طُوًى |
| 17 |
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079017.mp3
|
اذْهَبْ إِلَى فِرْعَوْنَ إِنَّهُ طَغَى |
| 18 |
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?» |
/content/ayah/audio/hudhaify/079018.mp3
|
فَقُلْ هَل لَّكَ إِلَى أَن تَزَكَّى |
| 19 |
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079019.mp3
|
وَأَهْدِيَكَ إِلَى رَبِّكَ فَتَخْشَى |
| 20 |
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079020.mp3
|
فَأَرَاهُ الْآيَةَ الْكُبْرَى |
| 21 |
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079021.mp3
|
فَكَذَّبَ وَعَصَى |
| 22 |
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079022.mp3
|
ثُمَّ أَدْبَرَ يَسْعَى |
| 23 |
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079023.mp3
|
فَحَشَرَ فَنَادَى |
| 24 |
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡» |
/content/ayah/audio/hudhaify/079024.mp3
|
فَقَالَ أَنَا رَبُّكُمُ الْأَعْلَى |
| 25 |
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079025.mp3
|
فَأَخَذَهُ اللَّهُ نَكَالَ الْآخِرَةِ وَالْأُولَى |
| 26 |
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079026.mp3
|
إِنَّ فِي ذَلِكَ لَعِبْرَةً لِّمَن يَخْشَى |
| 27 |
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079027.mp3
|
أَأَنتُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَمِ السَّمَاء بَنَاهَا |
| 28 |
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079028.mp3
|
رَفَعَ سَمْكَهَا فَسَوَّاهَا |
| 29 |
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079029.mp3
|
وَأَغْطَشَ لَيْلَهَا وَأَخْرَجَ ضُحَاهَا |
| 30 |
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079030.mp3
|
وَالْأَرْضَ بَعْدَ ذَلِكَ دَحَاهَا |
| 31 |
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079031.mp3
|
أَخْرَجَ مِنْهَا مَاءهَا وَمَرْعَاهَا |
| 32 |
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079032.mp3
|
وَالْجِبَالَ أَرْسَاهَا |
| 33 |
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079033.mp3
|
مَتَاعًا لَّكُمْ وَلِأَنْعَامِكُمْ |
| 34 |
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079034.mp3
|
فَإِذَا جَاءتِ الطَّامَّةُ الْكُبْرَى |
| 35 |
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079035.mp3
|
يَوْمَ يَتَذَكَّرُ الْإِنسَانُ مَا سَعَى |
| 36 |
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079036.mp3
|
وَبُرِّزَتِ الْجَحِيمُ لِمَن يَرَى |
| 37 |
የካደ ሰውማ፣ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079037.mp3
|
فَأَمَّا مَن طَغَى |
| 38 |
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079038.mp3
|
وَآثَرَ الْحَيَاةَ الدُّنْيَا |
| 39 |
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079039.mp3
|
فَإِنَّ الْجَحِيمَ هِيَ الْمَأْوَى |
| 40 |
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079040.mp3
|
وَأَمَّا مَنْ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِ وَنَهَى النَّفْسَ عَنِ الْهَوَى |
| 41 |
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079041.mp3
|
فَإِنَّ الْجَنَّةَ هِيَ الْمَأْوَى |
| 42 |
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079042.mp3
|
يَسْأَلُونَكَ عَنِ السَّاعَةِ أَيَّانَ مُرْسَاهَا |
| 43 |
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ? |
/content/ayah/audio/hudhaify/079043.mp3
|
فِيمَ أَنتَ مِن ذِكْرَاهَا |
| 44 |
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079044.mp3
|
إِلَى رَبِّكَ مُنتَهَاهَا |
| 45 |
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079045.mp3
|
إِنَّمَا أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخْشَاهَا |
| 46 |
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/079046.mp3
|
كَأَنَّهُمْ يَوْمَ يَرَوْنَهَا لَمْ يَلْبَثُوا إِلَّا عَشِيَّةً أَوْ ضُحَاهَا |