1 |
ወዳቂ ከኾነው ቅጣት ጠያቂ ጠየቀ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070001.mp3
|
سَأَلَ سَائِلٌ بِعَذَابٍ وَاقِعٍ |
2 |
በከሓዲዎች ላይ (ወዳቂ ከኾነው) ለእርሱ መላሽ የለውም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070002.mp3
|
لِّلْكَافِرينَ لَيْسَ لَهُ دَافِعٌ |
3 |
የ(ሰማያት) መሰላሎች ባለቤት ከኾነው አላህ (መላሽ የለውም)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070003.mp3
|
مِّنَ اللَّهِ ذِي الْمَعَارِجِ |
4 |
መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺሕ ዓመት በኾነ ቀን ውስጥ ወደእርሱ ያርጋሉ፤ (ይወጣሉ)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070004.mp3
|
تَعْرُجُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ إِلَيْهِ فِي يَوْمٍ كَانَ مِقْدَارُهُ خَمْسِينَ أَلْفَ سَنَةٍ |
5 |
መልካምንም ትዕግስት ታገሥ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070005.mp3
|
فَاصْبِرْ صَبْرًا جَمِيلًا |
6 |
እነርሱ (ያንን ቀን) ሩቅ አድርገው ያዩታል፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070006.mp3
|
إِنَّهُمْ يَرَوْنَهُ بَعِيدًا |
7 |
እኛም ቅርብ ኾኖ እናየዋለን፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070007.mp3
|
وَنَرَاهُ قَرِيبًا |
8 |
ሰማይ እንደ ዘይት አተላ በምትኾንበት ቀን፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070008.mp3
|
يَوْمَ تَكُونُ السَّمَاء كَالْمُهْلِ |
9 |
ጋራዎችም በተለያዩ ቀለማት እንደ ተነከረ ሱፍ (ነፋስ እንደሚያበረው) በሚኾኑበት ቀን፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070009.mp3
|
وَتَكُونُ الْجِبَالُ كَالْعِهْنِ |
10 |
ዘመድም ዘመድን በማይጠይቅበት ቀን፤ (መላሽ የለውም)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070010.mp3
|
وَلَا يَسْأَلُ حَمِيمٌ حَمِيمًا |
11 |
(ዘመዶቻቸውን) ያዩዋቸዋል፡፡ አመጸኛው ከዚያ ቀን ስቃይ (ነፍሱን) በልጆቹ ሊበዥ ይመኛል፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070011.mp3
|
يُبَصَّرُونَهُمْ يَوَدُّ الْمُجْرِمُ لَوْ يَفْتَدِي مِنْ عَذَابِ يَوْمِئِذٍ بِبَنِيهِ |
12 |
በሚስቱም በወንድሙም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070012.mp3
|
وَصَاحِبَتِهِ وَأَخِيهِ |
13 |
በዚያችም በምታስጠጋው ጎሳው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070013.mp3
|
وَفَصِيلَتِهِ الَّتِي تُؤْويهِ |
14 |
በምድርም ላይ ባለው ሁሉ (ሊበዥ) ከዚያም ሊያድነው (ይመኛል)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070014.mp3
|
وَمَن فِي الْأَرْضِ جَمِيعًا ثُمَّ يُنجِيهِ |
15 |
ይተው! እርሷ (እሳቲቱ) ለዟ ናት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070015.mp3
|
كَلَّا إِنَّهَا لَظَى |
16 |
የራስን ቅል ቆዳ የምትሞሽልቅ ስትኾን፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070016.mp3
|
نَزَّاعَةً لِّلشَّوَى |
17 |
(ከእምነት) የዞረንና የሸሸን ሰው (ወደእርሷ) ትጠራለች፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070017.mp3
|
تَدْعُو مَنْ أَدْبَرَ وَتَوَلَّى |
18 |
ገንዘብን የሰበሰበንና (ዘካውን ሳይሰጥ) የቆጠረንም፤ (ትጠራለች)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070018.mp3
|
وَجَمَعَ فَأَوْعَى |
19 |
ሰው ቅጠ ቢስ ኾኖ ተፈጠረ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070019.mp3
|
إِنَّ الْإِنسَانَ خُلِقَ هَلُوعًا |
20 |
ክፉ ነገር ባገኘው ጊዜ ብስጪተኛ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070020.mp3
|
إِذَا مَسَّهُ الشَّرُّ جَزُوعًا |
21 |
መልካምም ነገር (ድሎት) ባገኘ ጊዜ ከልካይ (ኾኖ ተፈጠረ)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070021.mp3
|
وَإِذَا مَسَّهُ الْخَيْرُ مَنُوعًا |
22 |
ሰጋጆቹ ብቻ ሲቀሩ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070022.mp3
|
إِلَّا الْمُصَلِّينَ |
23 |
እነዚያ እነርሱ በስግደታቸው ላይ ዘውታሪዎች የኾኑት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070023.mp3
|
الَّذِينَ هُمْ عَلَى صَلَاتِهِمْ دَائِمُونَ |
24 |
እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070024.mp3
|
وَالَّذِينَ فِي أَمْوَالِهِمْ حَقٌّ مَّعْلُومٌ |
25 |
ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070025.mp3
|
لِّلسَّائِلِ وَالْمَحْرُومِ |
26 |
እነዚያም በፍርዱ ቀን እውነት የሚሉት (የሚያረጋግጡት)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070026.mp3
|
وَالَّذِينَ يُصَدِّقُونَ بِيَوْمِ الدِّينِ |
27 |
እነዚያም እነርሱ ከጌታቸው ቅጣት ፈሪዎች የኾኑት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070027.mp3
|
وَالَّذِينَ هُم مِّنْ عَذَابِ رَبِّهِم مُّشْفِقُونَ |
28 |
የጌታቸው ቅጣት (መምጣቱ) የማያስተማምን ነውና፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070028.mp3
|
إِنَّ عَذَابَ رَبِّهِمْ غَيْرُ مَأْمُونٍ |
29 |
እነዚያም እነርሱ ብልቶቻቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070029.mp3
|
وَالَّذِينَ هُمْ لِفُرُوجِهِمْ حَافِظُونَ |
30 |
በሚስቶቻቸው ወይም እጆቻቸው በያዙዋቸው (ባሪያዎች) ላይ ሲቀር፡፡ እነርሱ (በእነዚህ) የማይወቀሱ ናቸውና፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070030.mp3
|
إِلَّا عَلَى أَزْوَاجِهِمْ أَوْ مَا مَلَكَتْ أَيْمَانُهُمْ فَإِنَّهُمْ غَيْرُ مَلُومِينَ |
31 |
ከዚያም ወዲያ የፈለገ ሰው እነዚያ እነሱ ድንበር አላፊዎች ናቸው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070031.mp3
|
فَمَنِ ابْتَغَى وَرَاء ذَلِكَ فَأُوْلَئِكَ هُمُ الْعَادُونَ |
32 |
እነዚያም እነርሱ አደራዎቻቸውንና ቃል ኪዳናቸውን ጠባቂዎች የኾኑት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070032.mp3
|
وَالَّذِينَ هُمْ لِأَمَانَاتِهِمْ وَعَهْدِهِمْ رَاعُونَ |
33 |
እነዚያም እነርሱ በምስክርነታቸው ትክክለኞች የኾኑት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070033.mp3
|
وَالَّذِينَ هُم بِشَهَادَاتِهِمْ قَائِمُونَ |
34 |
እነዚያም እነርሱ በሶላቶቻቸው ላይ የሚጠባበቁት፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070034.mp3
|
وَالَّذِينَ هُمْ عَلَى صَلَاتِهِمْ يُحَافِظُونَ |
35 |
እነዚህ (ከዚህ በላይ የተወሱት ሁሉ) በገነቶች ውስጥ የሚከበሩ ናቸው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070035.mp3
|
أُوْلَئِكَ فِي جَنَّاتٍ مُّكْرَمُونَ |
36 |
ለእነዚያም ለካዱት ወደ አንተ በኩል አንገቶቻቸውን መዝዘው የሚያተኩሩት ምን አላቸው? |
/content/ayah/audio/hudhaify/070036.mp3
|
فَمَالِ الَّذِينَ كَفَرُوا قِبَلَكَ مُهْطِعِينَ |
37 |
ከቀኝና ከግራ ክፍልፍል ጭፍሮች ሲኾኑ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070037.mp3
|
عَنِ الْيَمِينِ وَعَنِ الشِّمَالِ عِزِينَ |
38 |
ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው የጸጋይቱን ገነት መግባትን ይከጅላልን? |
/content/ayah/audio/hudhaify/070038.mp3
|
أَيَطْمَعُ كُلُّ امْرِئٍ مِّنْهُمْ أَن يُدْخَلَ جَنَّةَ نَعِيمٍ |
39 |
ይከልከል፤ እኛ ከሚያውቁት ነገር (ከፍቶት ጠብታ) ፈጠርናቸው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070039.mp3
|
كَلَّا إِنَّا خَلَقْنَاهُم مِّمَّا يَعْلَمُونَ |
40 |
በምሥራቆችና በምዕራቦችም ጌታ እምላለሁ፡፡ እኛ በእርግጥ ቻዮች ነን፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070040.mp3
|
فَلَا أُقْسِمُ بِرَبِّ الْمَشَارِقِ وَالْمَغَارِبِ إِنَّا لَقَادِرُونَ |
41 |
ከእነርሱ የተሻለን በመለወጥ ላይ፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070041.mp3
|
عَلَى أَن نُّبَدِّلَ خَيْرًا مِّنْهُمْ وَمَا نَحْنُ بِمَسْبُوقِينَ |
42 |
ያንንም የሚስፈራሩበትን ቀናቸውን እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው፡፡ ይዋኙ ይጫወቱም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070042.mp3
|
فَذَرْهُمْ يَخُوضُوا وَيَلْعَبُوا حَتَّى يُلَاقُوا يَوْمَهُمُ الَّذِي يُوعَدُونَ |
43 |
ወደ ጣዖቶች እንደሚሽቀዳደሙ ኾነው ከመቃብሮቻቸው ፈጥነው የሚወጡበትን ቀን (እስከሚገናኙ ድረስ ተዋቸው)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070043.mp3
|
يَوْمَ يَخْرُجُونَ مِنَ الْأَجْدَاثِ سِرَاعًا كَأَنَّهُمْ إِلَى نُصُبٍ يُوفِضُونَ |
44 |
ዓይኖቻቸው ያፈሩ ኾነው ውርደት ትሸፍናቸዋለች፡፡ ይህ ቀን ያ ይስፈራሩበት የነበሩት ነው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/070044.mp3
|
خَاشِعَةً أَبْصَارُهُمْ تَرْهَقُهُمْ ذِلَّةٌ ذَلِكَ الْيَوْمُ الَّذِي كَانُوا يُوعَدُونَ |