Al-Adiyat

Change Language
Change Surah
Change Recitation

Amharic: Muhammed Sadiq and Muhammed Sani Habib

Play All
# Translation Ayah
1 እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡ وَالْعَادِيَاتِ ضَبْحًا
2 (በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤ فَالْمُورِيَاتِ قَدْحًا
3 በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤ فَالْمُغِيرَاتِ صُبْحًا
4 በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤ فَأَثَرْنَ بِهِ نَقْعًا
5 በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡ فَوَسَطْنَ بِهِ جَمْعًا
6 ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡ إِنَّ الْإِنسَانَ لِرَبِّهِ لَكَنُودٌ
7 እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡ وَإِنَّهُ عَلَى ذَلِكَ لَشَهِيدٌ
8 እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡ وَإِنَّهُ لِحُبِّ الْخَيْرِ لَشَدِيدٌ
9 (ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤ أَفَلَا يَعْلَمُ إِذَا بُعْثِرَ مَا فِي الْقُبُورِ
10 በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡ وَحُصِّلَ مَا فِي الصُّدُورِ
11 ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡ إِنَّ رَبَّهُم بِهِمْ يَوْمَئِذٍ لَّخَبِيرٌ
;