1 |
(ነገሩ ከሓዲዎች እንደሚሉት) አይደለም፡፡ በትንሣኤ ቀን እምላለሁ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075001.mp3
|
لَا أُقْسِمُ بِيَوْمِ الْقِيَامَةِ |
2 |
(ራሷን) ወቃሽ በኾነች ነፍስም እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075002.mp3
|
وَلَا أُقْسِمُ بِالنَّفْسِ اللَّوَّامَةِ |
3 |
ሰው አጥንቶቹን አለመሰብሰባችንን ያስባልን? |
/content/ayah/audio/hudhaify/075003.mp3
|
أَيَحْسَبُ الْإِنسَانُ أَلَّن نَجْمَعَ عِظَامَهُ |
4 |
አይደለም ጣቶቹን (ፊት እንደ ነበሩ) በማስተካከል ላይ ቻዮች ስንኾን (እንሰበስባቸዋለን)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075004.mp3
|
بَلَى قَادِرِينَ عَلَى أَن نُّسَوِّيَ بَنَانَهُ |
5 |
ይልቁንም ሰው በፊቱ ባለው ነገር (በትንሣኤ) ሊያስተባብል ይፈልጋል፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075005.mp3
|
بَلْ يُرِيدُ الْإِنسَانُ لِيَفْجُرَ أَمَامَهُ |
6 |
«የትንሣኤው ቀን መቼ ነው?» ሲል ይጠይቃል፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075006.mp3
|
يَسْأَلُ أَيَّانَ يَوْمُ الْقِيَامَةِ |
7 |
ዓይንም በዋለለ ጊዜ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075007.mp3
|
فَإِذَا بَرِقَ الْبَصَرُ |
8 |
ጨረቃም በጨለመ ጊዜ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075008.mp3
|
وَخَسَفَ الْقَمَرُ |
9 |
ፀሐይና ጨረቃም በተሰበሰቡ ጊዜ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075009.mp3
|
وَجُمِعَ الشَّمْسُ وَالْقَمَرُ |
10 |
«ሰው በዚያ ቀን መሸሻው የት ነው?» ይላል፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075010.mp3
|
يَقُولُ الْإِنسَانُ يَوْمَئِذٍ أَيْنَ الْمَفَرُّ |
11 |
ይከልከል፤ ምንም መጠጊያ የለም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075011.mp3
|
كَلَّا لَا وَزَرَ |
12 |
በዚያ ቀን መርጊያው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075012.mp3
|
إِلَى رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ الْمُسْتَقَرُّ |
13 |
ሰው በዚያ ቀን ባስቀደመውና ባስቆየው ሁሉ ይነገራል፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075013.mp3
|
يُنَبَّأُ الْإِنسَانُ يَوْمَئِذٍ بِمَا قَدَّمَ وَأَخَّرَ |
14 |
በእርግጥም ሰው በነፍሱ ላይ አስረጅ ነው፡፡ (አካሎቹ ይመሰክሩበታል)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075014.mp3
|
بَلِ الْإِنسَانُ عَلَى نَفْسِهِ بَصِيرَةٌ |
15 |
ምክንያቶቹን ሁሉ ቢያመጣም እንኳ (አይሰማም)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075015.mp3
|
وَلَوْ أَلْقَى مَعَاذِيرَهُ |
16 |
በእርሱ (በቁርኣን ንባብ) ልትቸኩል ምላስህን በእርሱ አታላውስ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075016.mp3
|
لَا تُحَرِّكْ بِهِ لِسَانَكَ لِتَعْجَلَ بِهِ |
17 |
(በልብህ ውስጥ) መሰብሰቡና ማንበቡ በእኛ ላይ ነውና፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075017.mp3
|
إِنَّ عَلَيْنَا جَمْعَهُ وَقُرْآنَهُ |
18 |
ባነበብነውም ጊዜ (ካለቀ በኋላ) ንባቡን ተከተል፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075018.mp3
|
فَإِذَا قَرَأْنَاهُ فَاتَّبِعْ قُرْآنَهُ |
19 |
ከዚያም ማብራራቱ በእኛ ላይ ነው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075019.mp3
|
ثُمَّ إِنَّ عَلَيْنَا بَيَانَهُ |
20 |
(ከመጣደፍ) ተከልከል፡፡ ይልቁንም (ሰዎች) ፈጣኒቱን (ዓለም) ትወዳላችሁ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075020.mp3
|
كَلَّا بَلْ تُحِبُّونَ الْعَاجِلَةَ |
21 |
መጨረሻይቱንም (ዓለም) ትተዋላችሁ፡፡ (አትዘጋጁላትም)፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075021.mp3
|
وَتَذَرُونَ الْآخِرَةَ |
22 |
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075022.mp3
|
وُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ نَّاضِرَةٌ |
23 |
ወደ ጌታቸው ተመልካቾች ናቸው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075023.mp3
|
إِلَى رَبِّهَا نَاظِرَةٌ |
24 |
ፊቶችም በዚያ ቀን ጨፍጋጊዎች ናቸው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075024.mp3
|
وَوُجُوهٌ يَوْمَئِذٍ بَاسِرَةٌ |
25 |
በርሳቸውም ዐደጋ እንደሚሠራባቸው ያረጋግጣሉ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075025.mp3
|
تَظُنُّ أَن يُفْعَلَ بِهَا فَاقِرَةٌ |
26 |
ንቁ (ነፍስ) ብሪዎችን በደረሰች ጊዜ፤ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075026.mp3
|
كَلَّا إِذَا بَلَغَتْ التَّرَاقِيَ |
27 |
«አሻሪው ማነው?» በተባለም ጊዜ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075027.mp3
|
وَقِيلَ مَنْ رَاقٍ |
28 |
(ሕመምተኛው) እርሱ (የሰፈረበት ነገር ከዚህ ዓለም) መልለየት መኾኑን ባረጋገጠም ጊዜ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075028.mp3
|
وَظَنَّ أَنَّهُ الْفِرَاقُ |
29 |
ባትም በባት በተጣበቀች ጊዜ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075029.mp3
|
وَالْتَفَّتِ السَّاقُ بِالسَّاقِ |
30 |
በዚያ ቀን መነዳቱ ወደ ጌታህ (ፍርድ) ነው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075030.mp3
|
إِلَى رَبِّكَ يَوْمَئِذٍ الْمَسَاقُ |
31 |
አላመነምም አልሰገደምም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075031.mp3
|
فَلَا صَدَّقَ وَلَا صَلَّى |
32 |
ግን አስተባበለ፤ (ከእምነት) ዞረም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075032.mp3
|
وَلَكِن كَذَّبَ وَتَوَلَّى |
33 |
ከዚያም እየተንጎባለለ ወደ ቤተሰቡ ኼደ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075033.mp3
|
ثُمَّ ذَهَبَ إِلَى أَهْلِهِ يَتَمَطَّى |
34 |
የምትጠላውን ነገር (አላህ) ያስከትልህ፡፡ ለአንተ ተገቢህም ነው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075034.mp3
|
أَوْلَى لَكَ فَأَوْلَى |
35 |
ከዚያም ጥፋት ይጠጋህ ለአንተ የተገባህም ነው፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075035.mp3
|
ثُمَّ أَوْلَى لَكَ فَأَوْلَى |
36 |
ሰው ስድ ኾኖ መትተውን ይጠረጥራልን? |
/content/ayah/audio/hudhaify/075036.mp3
|
أَيَحْسَبُ الْإِنسَانُ أَن يُتْرَكَ سُدًى |
37 |
የሚፈሰስ ከኾነ የፍትወት ጠብታ አልነበረምን? |
/content/ayah/audio/hudhaify/075037.mp3
|
أَلَمْ يَكُ نُطْفَةً مِّن مَّنِيٍّ يُمْنَى |
38 |
ከዚያም የረጋ ደም ኾነ (አላህ ሰው አድርጎ) ፈጠረውም፡፡ አስተካከለውም፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075038.mp3
|
ثُمَّ كَانَ عَلَقَةً فَخَلَقَ فَسَوَّى |
39 |
ከእርሱም ሁለት ዓይነቶችን ወንድና ሴትን አደረገ፡፡ |
/content/ayah/audio/hudhaify/075039.mp3
|
فَجَعَلَ مِنْهُ الزَّوْجَيْنِ الذَّكَرَ وَالْأُنثَى |
40 |
ይህ (ጌታ) ሙታንን ሕያው በማድረግ ላይ ቻይ አይደለምን? |
/content/ayah/audio/hudhaify/075040.mp3
|
أَلَيْسَ ذَلِكَ بِقَادِرٍ عَلَى أَن يُحْيِيَ الْمَوْتَى |