As-Saffat

Change Language
Change Surah
Change Recitation

Amharic: Muhammed Sadiq and Muhammed Sani Habib

Play All
# Translation Ayah
1 መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡ وَالصَّافَّاتِ صَفًّا
2 መገሠጽንም በሚገሥጹት፤ فَالزَّاجِرَاتِ زَجْرًا
3 ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡ فَالتَّالِيَاتِ ذِكْرًا
4 አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡ إِنَّ إِلَهَكُمْ لَوَاحِدٌ
5 የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡ رَبُّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا وَرَبُّ الْمَشَارِقِ
6 እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡ إِنَّا زَيَّنَّا السَّمَاء الدُّنْيَا بِزِينَةٍ الْكَوَاكِبِ
7 አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡ وَحِفْظًا مِّن كُلِّ شَيْطَانٍ مَّارِدٍ
8 ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡ لَا يَسَّمَّعُونَ إِلَى الْمَلَإِ الْأَعْلَى وَيُقْذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٍ
9 የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡ دُحُورًا وَلَهُمْ عَذَابٌ وَاصِبٌ
10 ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡ إِلَّا مَنْ خَطِفَ الْخَطْفَةَ فَأَتْبَعَهُ شِهَابٌ ثَاقِبٌ
11 ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡ فَاسْتَفْتِهِمْ أَهُمْ أَشَدُّ خَلْقًا أَم مَّنْ خَلَقْنَا إِنَّا خَلَقْنَاهُم مِّن طِينٍ لَّازِبٍ
12 ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡ بَلْ عَجِبْتَ وَيَسْخَرُونَ
13 በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡ وَإِذَا ذُكِّرُوا لَا يَذْكُرُونَ
14 ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡ وَإِذَا رَأَوْا آيَةً يَسْتَسْخِرُونَ
15 ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ وَقَالُوا إِنْ هَذَا إِلَّا سِحْرٌ مُّبِينٌ
16 «በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን? أَئِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَامًا أَئِنَّا لَمَبْعُوثُونَ
17 «የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡ أَوَآبَاؤُنَا الْأَوَّلُونَ
18 «አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡ قُلْ نَعَمْ وَأَنتُمْ دَاخِرُونَ
19 እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡ فَإِنَّمَا هِيَ زَجْرَةٌ وَاحِدَةٌ فَإِذَا هُمْ يَنظُرُونَ
20 «ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡ وَقَالُوا يَا وَيْلَنَا هَذَا يَوْمُ الدِّينِ
21 «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡ هَذَا يَوْمُ الْفَصْلِ الَّذِي كُنتُمْ بِهِ تُكَذِّبُونَ
22 (ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡ احْشُرُوا الَّذِينَ ظَلَمُوا وَأَزْوَاجَهُمْ وَمَا كَانُوا يَعْبُدُونَ
23 «ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡ مِن دُونِ اللَّهِ فَاهْدُوهُمْ إِلَى صِرَاطِ الْجَحِيمِ
24 «አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡ وَقِفُوهُمْ إِنَّهُم مَّسْئُولُونَ
25 (ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡ مَا لَكُمْ لَا تَنَاصَرُونَ
26 በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡ بَلْ هُمُ الْيَوْمَ مُسْتَسْلِمُونَ
27 የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡ وَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَى بَعْضٍ يَتَسَاءلُونَ
28 (ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡ قَالُوا إِنَّكُمْ كُنتُمْ تَأْتُونَنَا عَنِ الْيَمِينِ
29 (አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡ قَالُوا بَل لَّمْ تَكُونُوا مُؤْمِنِينَ
30 «ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡ وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيْكُم مِّن سُلْطَانٍ بَلْ كُنتُمْ قَوْمًا طَاغِينَ
31 «በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡ فَحَقَّ عَلَيْنَا قَوْلُ رَبِّنَا إِنَّا لَذَائِقُونَ
32 «ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡ فَأَغْوَيْنَاكُمْ إِنَّا كُنَّا غَاوِينَ
33 ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ነጋሪዎች ናቸው፡፡ فَإِنَّهُمْ يَوْمَئِذٍ فِي الْعَذَابِ مُشْتَرِكُونَ
34 እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡ إِنَّا كَذَلِكَ نَفْعَلُ بِالْمُجْرِمِينَ
35 እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡ إِنَّهُمْ كَانُوا إِذَا قِيلَ لَهُمْ لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ يَسْتَكْبِرُونَ
36 እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡ وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوا آلِهَتِنَا لِشَاعِرٍ مَّجْنُونٍ
37 አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡ بَلْ جَاء بِالْحَقِّ وَصَدَّقَ الْمُرْسَلِينَ
38 እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡ إِنَّكُمْ لَذَائِقُو الْعَذَابِ الْأَلِيمِ
39 ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡ وَمَا تُجْزَوْنَ إِلَّا مَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ
40 ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡ إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ
41 እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡ أُوْلَئِكَ لَهُمْ رِزْقٌ مَّعْلُومٌ
42 ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤ فَوَاكِهُ وَهُم مُّكْرَمُونَ
43 በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡ فِي جَنَّاتِ النَّعِيمِ
44 ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ عَلَى سُرُرٍ مُّتَقَابِلِينَ
45 ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡ يُطَافُ عَلَيْهِم بِكَأْسٍ مِن مَّعِينٍ
46 ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡ بَيْضَاء لَذَّةٍ لِّلشَّارِبِينَ
47 በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡ لَا فِيهَا غَوْلٌ وَلَا هُمْ عَنْهَا يُنزَفُونَ
48 እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡ وَعِنْدَهُمْ قَاصِرَاتُ الطَّرْفِ عِينٌ
49 እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡ كَأَنَّهُنَّ بَيْضٌ مَّكْنُونٌ
50 የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡ فَأَقْبَلَ بَعْضُهُمْ عَلَى بَعْضٍ يَتَسَاءلُونَ
51 ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡ قَالَ قَائِلٌ مِّنْهُمْ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٌ
52 «በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡ يَقُولُ أَئِنَّكَ لَمِنْ الْمُصَدِّقِينَ
53 «በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡ أَئِذَا مِتْنَا وَكُنَّا تُرَابًا وَعِظَامًا أَئِنَّا لَمَدِينُونَ
54 እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡ قَالَ هَلْ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ
55 ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡ فَاطَّلَعَ فَرَآهُ فِي سَوَاء الْجَحِيمِ
56 ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡ قَالَ تَاللَّهِ إِنْ كِدتَّ لَتُرْدِينِ
57 «የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡» وَلَوْلَا نِعْمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ الْمُحْضَرِينَ
58 (የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን? أَفَمَا نَحْنُ بِمَيِّتِينَ
59 «የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡ إِلَّا مَوْتَتَنَا الْأُولَى وَمَا نَحْنُ بِمُعَذَّبِينَ
60 ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡ إِنَّ هَذَا لَهُوَ الْفَوْزُ الْعَظِيمُ
61 ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡ لِمِثْلِ هَذَا فَلْيَعْمَلْ الْعَامِلُونَ
62 በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ? أَذَلِكَ خَيْرٌ نُّزُلًا أَمْ شَجَرَةُ الزَّقُّومِ
63 እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡ إِنَّا جَعَلْنَاهَا فِتْنَةً لِّلظَّالِمِينَ
64 እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡ إِنَّهَا شَجَرَةٌ تَخْرُجُ فِي أَصْلِ الْجَحِيمِ
65 እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡ طَلْعُهَا كَأَنَّهُ رُؤُوسُ الشَّيَاطِينِ
66 እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡ فَإِنَّهُمْ لَآكِلُونَ مِنْهَا فَمَالِؤُونَ مِنْهَا الْبُطُونَ
67 ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡ ثُمَّ إِنَّ لَهُمْ عَلَيْهَا لَشَوْبًا مِّنْ حَمِيمٍ
68 ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡ ثُمَّ إِنَّ مَرْجِعَهُمْ لَإِلَى الْجَحِيمِ
69 እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡ إِنَّهُمْ أَلْفَوْا آبَاءهُمْ ضَالِّينَ
70 እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡ فَهُمْ عَلَى آثَارِهِمْ يُهْرَعُونَ
71 ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡ وَلَقَدْ ضَلَّ قَبْلَهُمْ أَكْثَرُ الْأَوَّلِينَ
72 በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡ وَلَقَدْ أَرْسَلْنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ
73 የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡ فَانظُرْ كَيْفَ كَانَ عَاقِبَةُ الْمُنذَرِينَ
74 ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡ إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ
75 ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን! وَلَقَدْ نَادَانَا نُوحٌ فَلَنِعْمَ الْمُجِيبُونَ
76 እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡ وَنَجَّيْنَاهُ وَأَهْلَهُ مِنَ الْكَرْبِ الْعَظِيمِ
77 ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤ وَجَعَلْنَا ذُرِّيَّتَهُ هُمْ الْبَاقِينَ
78 በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡ وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِي الْآخِرِينَ
79 «በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡» سَلَامٌ عَلَى نُوحٍ فِي الْعَالَمِينَ
80 እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡ إِنَّا كَذَلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ
81 እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡ إِنَّهُ مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ
82 ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡ ثُمَّ أَغْرَقْنَا الْآخَرِينَ
83 ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡ وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِ لَإِبْرَاهِيمَ
84 ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡ إِذْ جَاء رَبَّهُ بِقَلْبٍ سَلِيمٍ
85 «ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡ إِذْ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوْمِهِ مَاذَا تَعْبُدُونَ
86 «ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን? أَئِفْكًا آلِهَةً دُونَ اللَّهِ تُرِيدُونَ
87 «በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡ فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ الْعَالَمِينَ
88 በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡ فَنَظَرَ نَظْرَةً فِي النُّجُومِ
89 «እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡ فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٌ
90 ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡ فَتَوَلَّوْا عَنْهُ مُدْبِرِينَ
91 ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?» فَرَاغَ إِلَى آلِهَتِهِمْ فَقَالَ أَلَا تَأْكُلُونَ
92 «የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?» مَا لَكُمْ لَا تَنطِقُونَ
93 በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡ فَرَاغَ عَلَيْهِمْ ضَرْبًا بِالْيَمِينِ
94 ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡ فَأَقْبَلُوا إِلَيْهِ يَزِفُّونَ
95 አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?» قَالَ أَتَعْبُدُونَ مَا تَنْحِتُونَ
96 «አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡» وَاللَّهُ خَلَقَكُمْ وَمَا تَعْمَلُونَ
97 «ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡ قَالُوا ابْنُوا لَهُ بُنْيَانًا فَأَلْقُوهُ فِي الْجَحِيمِ
98 በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡ فَأَرَادُوا بِهِ كَيْدًا فَجَعَلْنَاهُمُ الْأَسْفَلِينَ
99 አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡» وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَى رَبِّي سَيَهْدِينِ
100 ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡ رَبِّ هَبْ لِي مِنَ الصَّالِحِينَ
101 ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡ فَبَشَّرْنَاهُ بِغُلَامٍ حَلِيمٍ
102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡ فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ السَّعْيَ قَالَ يَا بُنَيَّ إِنِّي أَرَى فِي الْمَنَامِ أَنِّي أَذْبَحُكَ فَانظُرْ مَاذَا تَرَى قَالَ يَا أَبَتِ افْعَلْ مَا تُؤْمَرُ سَتَجِدُنِي إِن شَاء اللَّهُ مِنَ الصَّابِرِينَ
103 ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡ فَلَمَّا أَسْلَمَا وَتَلَّهُ لِلْجَبِينِ
104 ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ! وَنَادَيْنَاهُ أَنْ يَا إِبْرَاهِيمُ
105 ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡ قَدْ صَدَّقْتَ الرُّؤْيَا إِنَّا كَذَلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ
106 ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡ إِنَّ هَذَا لَهُوَ الْبَلَاء الْمُبِينُ
107 በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡ وَفَدَيْنَاهُ بِذِبْحٍ عَظِيمٍ
108 በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡ وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِي الْآخِرِينَ
109 ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡ سَلَامٌ عَلَى إِبْرَاهِيمَ
110 እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡ كَذَلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ
111 እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡ إِنَّهُ مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ
112 በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡ وَبَشَّرْنَاهُ بِإِسْحَاقَ نَبِيًّا مِّنَ الصَّالِحِينَ
113 በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡ وَبَارَكْنَا عَلَيْهِ وَعَلَى إِسْحَاقَ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحْسِنٌ وَظَالِمٌ لِّنَفْسِهِ مُبِينٌ
114 በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡ وَلَقَدْ مَنَنَّا عَلَى مُوسَى وَهَارُونَ
115 እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡ وَنَجَّيْنَاهُمَا وَقَوْمَهُمَا مِنَ الْكَرْبِ الْعَظِيمِ
116 ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡ وَنَصَرْنَاهُمْ فَكَانُوا هُمُ الْغَالِبِينَ
117 በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡ وَآتَيْنَاهُمَا الْكِتَابَ الْمُسْتَبِينَ
118 ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡ وَهَدَيْنَاهُمَا الصِّرَاطَ الْمُسْتَقِيمَ
119 በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡ وَتَرَكْنَا عَلَيْهِمَا فِي الْآخِرِينَ
120 ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡ سَلَامٌ عَلَى مُوسَى وَهَارُونَ
121 እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡ إِنَّا كَذَلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ
122 ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡ إِنَّهُمَا مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ
123 ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡ وَإِنَّ إِلْيَاسَ لَمِنْ الْمُرْسَلِينَ
124 ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን? إِذْ قَالَ لِقَوْمِهِ أَلَا تَتَّقُونَ
125 በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን? أَتَدْعُونَ بَعْلًا وَتَذَرُونَ أَحْسَنَ الْخَالِقِينَ
126 አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)? وَاللَّهَ رَبَّكُمْ وَرَبَّ آبَائِكُمُ الْأَوَّلِينَ
127 አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡ فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمْ لَمُحْضَرُونَ
128 ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡ إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ
129 በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡ وَتَرَكْنَا عَلَيْهِ فِي الْآخِرِينَ
130 ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡ سَلَامٌ عَلَى إِلْ يَاسِينَ
131 እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡ إِنَّا كَذَلِكَ نَجْزِي الْمُحْسِنِينَ
132 እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡ إِنَّهُ مِنْ عِبَادِنَا الْمُؤْمِنِينَ
133 ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡ وَإِنَّ لُوطًا لَّمِنَ الْمُرْسَلِينَ
134 እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡ إِذْ نَجَّيْنَاهُ وَأَهْلَهُ أَجْمَعِينَ
135 (በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡ إِلَّا عَجُوزًا فِي الْغَابِرِينَ
136 ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡ ثُمَّ دَمَّرْنَا الْآخَرِينَ
137 እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡ وَإِنَّكُمْ لَتَمُرُّونَ عَلَيْهِم مُّصْبِحِينَ
138 በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን? وَبِاللَّيْلِ أَفَلَا تَعْقِلُونَ
139 ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡ وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ الْمُرْسَلِينَ
140 ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ إِذْ أَبَقَ إِلَى الْفُلْكِ الْمَشْحُونِ
141 ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡ فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنْ الْمُدْحَضِينَ
142 እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡ فَالْتَقَمَهُ الْحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٌ
143 እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤ فَلَوْلَا أَنَّهُ كَانَ مِنْ الْمُسَبِّحِينَ
144 እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡ لَلَبِثَ فِي بَطْنِهِ إِلَى يَوْمِ يُبْعَثُونَ
145 እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡ فَنَبَذْنَاهُ بِالْعَرَاء وَهُوَ سَقِيمٌ
146 በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡ وَأَنبَتْنَا عَلَيْهِ شَجَرَةً مِّن يَقْطِينٍ
147 ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ፡፡ وَأَرْسَلْنَاهُ إِلَى مِئَةِ أَلْفٍ أَوْ يَزِيدُونَ
148 አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡ فَآمَنُوا فَمَتَّعْنَاهُمْ إِلَى حِينٍ
149 (የመካን ሰዎች) ጠይቃቸውም፡፡ «ለጌታህ ሴቶች ልጆች ለእነርሱም ወንዶች ልጆች ይኖራልን?» فَاسْتَفْتِهِمْ أَلِرَبِّكَ الْبَنَاتُ وَلَهُمُ الْبَنُونَ
150 ወይስ እኛ እነርሱ የተጣዱ ሆነው መላእክትን ሴቶች አድርገን ፈጠርን? أَمْ خَلَقْنَا الْمَلَائِكَةَ إِنَاثًا وَهُمْ شَاهِدُونَ
151 ንቁ! እነርሱ ከቅጥፈታቸው (የተነሳ) ይላሉ፡- أَلَا إِنَّهُم مِّنْ إِفْكِهِمْ لَيَقُولُونَ
152 «አላህ (መላእክትን) ወለደ፡፡» እነርሱም በእርግጥ ውሸታሞች ናቸው፡፡ وَلَدَ اللَّهُ وَإِنَّهُمْ لَكَاذِبُونَ
153 በወንዶች ልጆች ላይ ይልቅ ሴቶችን ልጆች መረጥን? أَصْطَفَى الْبَنَاتِ عَلَى الْبَنِينَ
154 ለእናንተ ምን (አስረጅ) አላችሁ? እንዴት ትፈርዳላችሁ! مَا لَكُمْ كَيْفَ تَحْكُمُونَ
155 አትገነዘቡምን? أَفَلَا تَذَكَّرُونَ
156 ወይስ ለእናንተ ግልጽ አስረጅ አላችሁን? أَمْ لَكُمْ سُلْطَانٌ مُّبِينٌ
157 «እውነተኞች እንደ ሆናችሁ መጽሐፋችሁን አምጡ» (በላቸው)፡፡ فَأْتُوا بِكِتَابِكُمْ إِن كُنتُمْ صَادِقِينَ
158 በአላህና በአጋንንት መካከልም ዝምድናን አደረጉ፡፡ አጋንንትም እነርሱ (ይህን ባዮች በእሳት) የሚጣዱ መሆናቸውን በእርግጥ ዐውቀዋል፡፡ وَجَعَلُوا بَيْنَهُ وَبَيْنَ الْجِنَّةِ نَسَبًا وَلَقَدْ عَلِمَتِ الْجِنَّةُ إِنَّهُمْ لَمُحْضَرُونَ
159 አላህ ከሚመጥኑት ሁሉ ጠራ፡፡ سُبْحَانَ اللَّهِ عَمَّا يَصِفُونَ
160 ግን የተመረጡት የአላህ ባሮች (በአላህ ላይ አይዋሹም)፡፡ إِلَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ
161 እናንተም የምትገዟቸውም ሁሉ፤ فَإِنَّكُمْ وَمَا تَعْبُدُونَ
162 በእርሱ (በአላህ) ላይ አንድንም አጥማሚዎች አይደላችሁም፡፡ مَا أَنتُمْ عَلَيْهِ بِفَاتِنِينَ
163 ያንን እርሱ ገሀነምን ገቢ የሆነውን ሰው ቢሆን እንጅ፡፡ إِلَّا مَنْ هُوَ صَالِ الْجَحِيمِ
164 (ጂብሪል አለ) ከእኛም አንድም የለም፤ ለእርሱ የታወቀ ደረጃ ያለው ቢሆን እንጅ፡፡ وَمَا مِنَّا إِلَّا لَهُ مَقَامٌ مَّعْلُومٌ
165 እኛም (ጌታን ለመግገዛት) ተሰላፊዎቹ እኛ ነን፡፡ وَإِنَّا لَنَحْنُ الصَّافُّونَ
166 እኛም (አላህን) አጥሪዎቹ እኛ ነን፡፡ وَإِنَّا لَنَحْنُ الْمُسَبِّحُونَ
167 እነርሱም (ከሓዲዎቹ) በእርግጥ ይሉ ነበሩ፡- وَإِنْ كَانُوا لَيَقُولُونَ
168 «ከቀድሞዎቹ (መጻሕፍት) ገሳጭ መጽሐፍ እኛ ዘንድ በነበረን ኖሮ፤ لَوْ أَنَّ عِندَنَا ذِكْرًا مِّنْ الْأَوَّلِينَ
169 «የአላህ ምርጦች ባሮች በሆን ነበር፡፡» لَكُنَّا عِبَادَ اللَّهِ الْمُخْلَصِينَ
170 ግን (ቁርኣኑ በመጣላቸው ጊዜ) በእርሱ ካዱ፡፡ ወደፊትም በእርግጥ ያውቃሉ፡፡ فَكَفَرُوا بِهِ فَسَوْفَ يَعْلَمُونَ
171 (የእርዳታ) ቃላችንም መልክተኞች ለሆኑት ባሮቻችን በእውነት አልፋለች፡፡ وَلَقَدْ سَبَقَتْ كَلِمَتُنَا لِعِبَادِنَا الْمُرْسَلِينَ
172 እነርሱ ተረጂዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡ إِنَّهُمْ لَهُمُ الْمَنصُورُونَ
173 ሰራዊቶቻችንም በእርግጥ አሸናፊዎቹ እነርሱ ናቸው፡፡ وَإِنَّ جُندَنَا لَهُمُ الْغَالِبُونَ
174 ከእነርሱም (ከመካ ከሓዲዎች) እስከ ጥቂት ጊዜ ድረስ ዙር (ተዋቸው)፡፡ فَتَوَلَّ عَنْهُمْ حَتَّى حِينٍ
175 እያቸውም ወደፊትም (የሚደርስባቸውን) ያያሉ፡፡ وَأَبْصِرْهُمْ فَسَوْفَ يُبْصِرُونَ
176 በቅጣታችንም ያቻኩላሉን? أَفَبِعَذَابِنَا يَسْتَعْجِلُونَ
177 በቀያቸውም በወረደ ጊዜ የተስፈራሪዎቹ ንጋት ከፋ! فَإِذَا نَزَلَ بِسَاحَتِهِمْ فَسَاء صَبَاحُ الْمُنذَرِينَ
178 እነርሱንም እስከ (ጥቂት) ጊዜ ድረስ ተዋቸው፡፡ وَتَوَلَّ عَنْهُمْ حَتَّى حِينٍ
179 ተመልከትም በእርግጥም ያያሉ፡፡ وَأَبْصِرْ فَسَوْفَ يُبْصِرُونَ
180 የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ سُبْحَانَ رَبِّكَ رَبِّ الْعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ
181 በመልክተኞቹም ላይ ሰላም ይኹኑ፤ وَسَلَامٌ عَلَى الْمُرْسَلِينَ
182 ምስጋናም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ይሁን፡፡ وَالْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ
;